Fana: At a Speed of Life!

አቶ ደመቀ መኮንን ከጃፓን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ታካጊ ኬይ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 10 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከጃፓን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ታካጊ ኬይ ጋር ተወያይተዋል።

በወይይታቸውም ሁለቱ ሀገራት በትምህርት እና በጤና ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።

በቀጣይም በሁለትዮሽ የግንኙነት ማዕቀፍ ውስጥ የሁለቱን ሀገራት ትብብር ለማጠናከር እንደሚሠራ መገለጹን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.