Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ኢትዮጵያ በቱርክ በደረሰው አደጋ የቁሳቁስ እና የነፍስ አድን ቡድን ለቱርክ ማበርከቷን አስታወቁ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 10 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቱርክ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ኢትዮጵያ ባላት አቅም የቁሳቁስ እና የነፍስ አድን ቡድን ለቱርክ ማበርከቷን አስታወቁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቱርክ ለደረሰው የሰው ህይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ በቱርክ በመሬት መንቀጥቀጥ በጠፋው የሰው ሕይወት እና በወደመው ንብረት የተሰማኝን ጥልቅ ኀዘን ለፕሬዚዳንት ሬሲፕ ታይፕ ኤርዶኻን ገልጫለሁ ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ የተቸገረ ወዳጇን ለመርዳት ምንጊዜም ቁርጠኛ ናት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባላት አቅም የቁሳቁስ እና የነፍስ አድን ቡድን ለቱርክ ማበርከቷን ገልፀዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.