Fana: At a Speed of Life!

ለኢትዮጵያና ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት የማደርገው ድጋፍ ይቀጥላል – ተመድ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ለኢትዮጵያና ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ፡፡

ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡

ዋና ጸሐፊው በውይይታቸው ላይ እየተሻሻለ የመጣውን የኢትዮጵያን የሰላም ሂደት አድንቀዋል።

ድጅቱ ለኢትዮጵያና ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል፡፡

የድርጅቱ መሥራች አባል ከሆነችው ኢትዮጵያ ጋር ያለውን የቆየ የትብብር ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እንሠራለን ብለዋ ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.