በሴቶች እኩልነት ዙሪያ በትኩረት ሊሰራ ይገባል- ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው
አዲስ አበባ፣ የካቲት 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሴቶች እኩልነት ዙሪያ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ተናገሩ፡፡
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በቀዳማዊ እመቤቶች መደበኛ ስብሰባ ላይ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል፡፡
በንግግራቸውም÷ በፆታ እኩልነት በኩል የሚታየውን ክፍተት ለማጥበብ ሴቶች ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
27ኛው መደበኛ የአፍሪካ ቀዳማዊ እመቤቶች አጠቃላይ መደበኛ ስብሰባ ከየካቲት 8 ጀምሮ እየተካሄደ መሆኑን ከቀዳማዊት እመቤት ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል::