ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በሰላም እንዲጠናቀቅ ያደረጉ ባለድርሻ አካላትን አመሰገኑ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ 36ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በሰላም እንዲጠናቀቅ ላደረጉ ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቀረቡ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት÷ “36ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ በሰላም እንዲጠናቀቅ ያደረጉ ባለድርሻ አካላትን ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች።” ብለዋል።