ዶ/ር ፍጹም አሰፋ ከተመድ የልማት ፕሮግራም የአፍሪካ ቢሮ ሃላፊ ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም የአፍሪካ ቢሮ ሃላፊ አሁና ኢዚያኮንዋ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ሚኒስትሯ የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም( ዩ ኤን ዲ ፒ) በኢትዮጵያ የሚከናወኑ የልማት ተግባራትን በመደገፍ ለሚያሳየው አጋርነት ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የልማት ፕሮግራሙ በኢትዮጵያ ልማቶች ላይ የሚያደርገው ተሳትፎ ሁልጊዜም ወጥነት ያለው መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሯ÷ ይህም በልዩ ልዩ የልማት መስኮች ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡
አሁና ኢዚያኮንዋ በበኩላቸው÷ ኢትዮጵያ የስንዴ ምርትን ኤክስፖርት ማድረግ በመጀመሯ መደሰታቸውን ገልጸው÷ለኢትዮጵያ ሕዝብና መንግስት እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡
የልማት ፕሮግራሙ ለኢትዮጵያ መንግስት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ማረጋገጣቸውንም ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡