ከንቲባ አዳነች በኢትዮጵያ የብራዚል አምባሳደር ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በኢትዮጵያ የብራዚል አምባሳደር ከሆኑት ጃንድራ ፌሬር ዶሳንቶስ ጋር ተወያዩ፡፡
በውይይታቸውም÷ አዲስ አበባ ከብራዚል ከተሞች ጋር በጋራ በምትሰራባቸው መንገዶች ላይ መክረዋል፡፡
ከንቲባ አዳነች በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷በሚላን “አርባን ፉድ ፖሊሲ ፕሮግራም” ላይ ለተሰጠን እውቅና እና ለተደረገልን አቀባበል እናመሰግናለን ብለዋል፡፡