Fana: At a Speed of Life!

8ኛው የአፍሪካ ተማሪዎች ምገባ ቀን ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ይከበራል

አዲስ አበባ፣ የካቲት 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)8ኛው የአፍሪካ የተማሪዎች ምገባ ቀን አዲስ አበባ በሚገኘው የአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ እንደሚከበር ተገለጸ፡፡

ቀኑን በማስመልከት ” የምግብ ግዥ ሥርዓቶችን እና የዕሴት ሰንሰለቶችን ማሳደግ የአፍሪካውያን አኅጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ሚና ለዘላቂ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራሞች እና ለተሻሻለ ትምህርት” በሚሉ መሪ ቃሎች በበይነ-መረብ ውይይት ይካሄዳል።

ውይይቱ በፈረንጆቹ የፊታችን የካቲት 27 እንደሚጀመርና እስከ መጋቢት 1 ቀን 2023 እንደሚቆይ ከአፍሪካ ኅብረት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

መርሃ ግብሩ በአዲስ አበባ አፍሪካ ኅብረት አዳራሽ እና በሞሮኮ ማራካሽ ይካሄዳል ነው የተባለው፡፡

በመድረኩ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ÷ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ÷ የትምህርት፣ ሣይንስ ፣ ቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ኮሚሽነር የሆኑት አልጄሪያዊው ፕሮፌሰር ሞሐመድ ቤልሆሲን ፣ የዓለም የምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቤስሊ ÷ እንዲሁም የሌሎች የተመድ ኤጀንሲዎች ተወካዮች ንግግር ያደርጋሉ ተብሏል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.