Fana: At a Speed of Life!

የሐረሪ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 2ኛ ዓመት 3ኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀምሯል።

በጉባዔው የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት የ2015 በጀት ዓመት የ6 ወራት አፈጻጸም ሪፖርት በርዕሠ መስተዳድሩ እንደሚቀርብ ተመላክቷል ፡፡

በምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አባላት በመስክ የተገመገሙና በካፒታል በጀት የተከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶችም ገለፃ እንደሚደረግባቸው ይጠበቃል፡፡

የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኦርዲን በድሪ፥ ያለፉት ሥድሥት ወራት አፈፃፀምን ካቀረቡ በኋላ በምክር ቤቱ እንደሚያፀድቁ ም ይጠበቃል።

በኢዮናዳብ አንዱዓለም

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.