Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በሠራተኞችና የሥራ ቅጥር ዙሪያ በጋራ ለመስራት ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በሠራተኞችና የሥራ ቅጥር ዙሪያ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል፡፡

የሥራና ክኅሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ከሶማሊያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ የሠራተኛ እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ቢህ ኢማን ጋር ተወያይተዋል፡፡

ሁለተኛው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) የሚኒስትሮች ጉባዔ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡

ከጉባዔው ጎን ለጎን በተፈጠረው መድረክም ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በሠራተኞች ሥራ፣ የሥራ ቅጥር እና የጉልበት ፍልሠት ዙሪያ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.