Fana: At a Speed of Life!

አዋሽ ባንክ በቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች 30 ሚሊየን ብር ለገሰ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 24 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አዋሽ ባንክ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች የ30 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል።

አዋሽ ባንክ ባለፈው ዓመትም በቦረና እና ጉጂ ዞኖች በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች60 ሚሊየን ብር መለገሱን የባንኩ መረጃ ያመላክታል።

ባንኩ ከዚህ ቀደም በምዕራብ ኦሮሚያ ተከስቶ በነበረው ግጭት ተፈናቅለው ለነበሩ ዜጎችና በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ንፋስ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ ቤት ለፈረሰባቸዉ አባወራዎችም የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.