ቻይና የነዳጅና ጋዝ ክምችት ማግኘቷን አስታወቀች
አዲስ አበባ ፣ የካቲት 25 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና ሰፊ የነዳጅና ጋዝ ክምችት ማግኘቷን አስታወቀች።
የሃገሪቱ የነዳጅ ዘይት እና ጋዝ ኮርፖሬሽን እንዳስታወቀው ክምችቱ፥ በቦሃይ ባህር በሚገኘው ቦዦንግ 26-6 የነዳጅ ማውጫ ስፍራ የተገኘ ነው።
አሁን ድፍድፍ ነዳጅ የተገኘበት ስፍራ የነዳጅ ክምችት ያለበት ሶስተኛው ስፍራ እንደሆነ መገለጹን አር ቲ ዘግቧል።
በስፍራው 100 ሚሊየን ቶን ቀላል የድፍድፍ ነዳጅ ክምችት መገኘቱንም ነው ኮርፖሬሽኑ ያስታወቀው።
ድፍድፍ ነዳጁ በተገኘበት ስፍራም አስፈላጊው ቁፋሮ መደረጉንም ኮርፖሬሽኑ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
በስፍራው በተደረገው ሙከራም 2 ሺህ 40 በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ እና 11 ነጥብ 45 ሚሊየን ኪዩቢክ ጫማ የተፈጥሮ ጋዝ በቀን ማምረት እንደሚቻል ኮርፖሬሽን ገልጿል።