በኦሮሚያ ክልል 1 ሺህ 21 አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ተሸጋገሩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል አነስተኛ እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ የማሸጋገር ሥነ-ሥርዓት በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡
በመድረኩ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ እና የሥራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፊሪሃት ካሚል እንዲሁም የክልሉና የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በሥነ-ሥርዓቱ 1 ሺህ 21 አነስተኛ እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ መሸጋገራቸውን የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡