Fana: At a Speed of Life!

የደቡብ ኮሪያ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ላይ እንዲሰማሩ የሚያስችል ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ከደቡብ ኮሪያ የዓለም አቀፍ ወጣቶች ህብረት ዋና ጸሃፊ ሁን ሞክ ሊ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም በአምራች ኢንዱስትሪው  ዘርፍ እና በተያያዥ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፉ በተለይም በጫማ ስራ ላይ የተሰማሩ የኮሪያ ባለሃብቶችን በኢትዮጵያ ውስጥ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ የሚያስችሉ ስራዎች እንደሚሰሩ ተገልጿል፡፡

በተጨማሪም ዘርፉን ሊያነቃቁ የሚችሉ “የማይንድ ሴት” ስልጠናን አጠናክሮ ማስቀጠል የሚያስችል ስምምነት ላይ  መድረሳቸው ተጠቁሟል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.