Fana: At a Speed of Life!

የኖርዌይ ሕዝብ ከዩኒሴፍ ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ በድርቅ ለተጎዱ ሕጻናት የሚውል 10 ቶን አስቸኳይ ድጋፍ ሊያደርስ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የኖርዌይ ሕዝብ ከተመድ ዓለም አቀፍ የሕፃናት መርጃ ድርጅት(ዩኒሴፍ) ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ በድርቅ ለተጎዱ ሕጻናት የሚውል 10 ቶን አስቸኳይ ድጋፍ ሊያደርስ መሆኑ ተገለጸ፡፡

የኖርዌይ ዕርዳታ ጫኝ አውሮፕላን 10 ቶን አስቸኳይ ድጋፍ ይዞ ከዴንማርክ መነሳቱ ተጠቁሟል፡፡

አውሮፕላኑ የሕክምና ቁሳቁስ፣ የንፅሕና መጠበቂያዎችን እና ሌሎች የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦቶችን ኮፐንሀገን ከሚገኘው ትልቁ የ“ዩኒሴፍ” ዓለም አቀፍ አፋጣኝ የዕርዳታ አቅርቦት እና ሎጅስቲክስ መጋዘን መጫኑን አቪየሽን 24 ዘግቧል፡፡

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ከ20 ሚሊየን የሚልቁ ሕፃናት የአስቸኳይ ሰብአዊ ዕርዳታ ያስፈልጋቸዋል ተብሏል።

በዮናታን ዮሴፍ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.