ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በጅማ ለሚገነባው የፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን አለም አቀፍ ሆቴል ግንባታ አስጀመሩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በጅማ ከተማ ለሚገነባው የፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን አለም አቀፍ ሆቴል የመሰረት ድንጋይ አስቀመጡ።
ሆቴሉ በ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር የሚገነባ ሲሆን ፥ ግንባታው በ4 ዓመታት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ተነግሯል።
የሆቴሉ ግንባታ በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የሚካሄድ ሲሆን ፥ በማሪዮት ኢንተርናሽናል ስታንደርድ መሰረት እንደሚከናወን ኢዜአ ዘግቧል።