Fana: At a Speed of Life!

ብሮሚን እና ክሮሊን ማዕድናት በቅርቡ ለውጭና ለሀገር ውስጥ ገበያ ሊቀርቡ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሮሚን እና የክሮሊን የማዕድን ምርቶች በቅርቡ ለውጭ እና ለሀገር ውስጥ ገበያ እንደሚውሉ የማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ።

የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ ሚሊዮን ማቴዎስ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን እንደገለጹት ÷ በአፋር አካባቢ ጨዋማ ባህሪ ያለውን የብሮሚን እና የክሮሊን የማዕድን ምርቶች በተጠናከረ መንገድ የማምረት ሥራ ተጀምሯል፡፡

ምርቶቹን በቅርቡ ለውጭና ለሀገር ውስጥ ገበያ ለማዋል እንቅስቃሴ ላይ መሆናቸውንም ነው የተናገሩት።

በሌሎች አካባቢዎችም አዳዲስ የማዕድን ሐብቶችን ወደ ምርት ለማስገባት ሚኒስቴሩ በተጠናከረ መንገድ እየሠራ መሆኑንም ገልጸዋል።

በተጨማሪም የተለያዩ ጌጣጌጦችን እና አዳዲስ የማዕድናት ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬ ለማስገኘት በሂደት ላይ መሆናቸውን አክለዋል።

በዋናነት ዘርፉን የማዘመን ስራ እየተሠራ እንደሆነም ተጠቁሟል።

በታሪክ አዱኛ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.