የአፍሪካ ቀጠናዊ የሠራተኛ አስተዳደር ማዕከል ጉባዔ የአባል ሀገራቱ ሚኒስትሮች በተገኙበት ተጀመረ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 49ኛው የአፍሪካ ቀጠናዊ የሠራተኛ አስተዳደር ማዕከል ጉባዔ የአባል ሀገራቱ ሚኒስትሮች በተገኙበት በአዲስ አበባ በይፋ ተከፍቷል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴዔታ አሰግድ ጌታቸው÷የኢትዮጵያ መንግስት የሠራተኛ አስተዳደር ሀገራዊ የልማት ግቦችን ለማሳካት መሰረታዊ መሆኑን ይገነዘባል ብለዋል፡፡
ማዕከሉ አፍሪካውያን የጋራ የሆኑ የሠራተኛ አስተዳደር ችግሮቻቸውን እንዲፈቱ ትልቅ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡