Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ ከነገ ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ታገደ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ከነገ ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የባለ ሦስት እና አራት እግር ባጃጅ ተሽከርካሪዎችን ማሽከርከር እንደማይቻል የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ፡፡

ከቢሮው ያገኘነው መረጃ እንዳመላከተው÷ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥን በተሻለ መልክ ለመምራት የሚያስችል የአሰራር ማሻሻያ ስራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡

በመሆኑም የአሰራር ማሻሻያው ተጠናቆ እና የአገልግሎቱ አስፈላጊነት በዝርዝር ተጠንቶ ውሳኔ እስከሚያገኝ ድረስ÷ ከነገ የካቲት 30 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በከተማዋ በየትኛውም አካባቢ ላልተወሰነ ጊዜ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት የታገደ መሆኑን ነው ቢሮው የገለጸው፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.