Fana: At a Speed of Life!

በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ18 ሺህ በለጠ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 3 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ)  በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 18 ሺህ 860  መድረሱ ተገለፀ።

ይህንም ተከትሎ አሜሪካ ከጣሊያን በላይ በርካታ ሰው በኮሮና ቫይረስ የሞተባት ሀገር በመሆን የአለም የኮሮና ወረርሽና ዋና ቦታ ሆናለች።

ሀገሪቱ በአለም በኮሮና ቫይርስ ከፍተኛ ቁጥር የተመዘገበባት ሀገር ልትሆን የቻለቸው በኒውዮርክ በዛሬው እለት ብቻ 783 ሞት መመዝገቡን ተከትሎ መሆኑን ብሎምበርግ ዘግቧል።

አሜሪካ ቀድማ በብዛት የኮሮና ቫይረስ ምርመራ አለማድረጓ እና አካላዊ ፈቃቅታ በበቂ ሁኔታ ባለማድረጓ በቫይረሱ ከፍተኛ ቀጥር ያለው ህዝብ እንድታጣ እድርጓታል ተብሏል።

በተመሳሳይ በብሪታኒያኒያ በአንድ ቀን የ917 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ በሀገሪቱ በቫይረሱ ምክንያት የሞቱት ሰዎች ቁጥር 9 ሺህ 875 ደርሷል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.