Fana: At a Speed of Life!

87 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከጅቡቲ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 87 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከጅቡቲ ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።

ኤምባሲው ከዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ጋር በመተባበር ነው ኢትዮጵያውያኑ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ያደረገው፡፡

ወደ ሀገራቸው ከተመለሱት 87 ስደተኞች መካከል 20 የሚሆኑት በህገ ወጥ መንገድ ከየመን ወደ ጅቡቲ የገቡ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

ቀሪዎቹ 67 ኢትዮጵያውያን ደግሞ ወደ የመን ለመግባት በሚያደርጉት ጉዞ በህገ ወጥ ደላላዎች እጅ ወድቀው አስከፊ እንግልት እንደደረሰባቸው ተመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.