Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከፓኪስታን ባለሃብቶች ጋር የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረመ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 5 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከፓኪስታን ባለሃብቶች ጋር የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረመ።

የመግባቢያ ሥምምነቱ የፋርማሲዩቲካልስ፣ የማሸጊያ ምርቶች ፋብሪካ እና የኢንዱስትሪ ፓርክ ማሳደግ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

አሁን የተፈረመው ሥምምነት የፓኪስታን ባለሃብቶች ቡድን በኢትዮጵያ እያደረገ ያለው ጉብኝት አካል መሆኑን የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል።

ሥምምነቱ የፓኪስታን ባለሃብቶች በቂሊንጦ እና ቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርኮች የፋርማሲዩቲካልስ እና የማሸጊያ ምርቶች ማምረቻ ፋብሪካ እንዲገነቡ የሚያስችል ነው ተብሏል።

የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነሯ ሌሊሴ ነሜ መንግስት የፓኪስታን ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ያላቸውን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።

የተፈረመው የመግባቢያ ሥምምነትም በኮሚሽኑና በፓኪስታን ባለሃብቶች መካከል ዘላቂ ትብብር ለመመስረት እንደሚያስችልም ነው የገለጹት።

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.