የደቡብ ምዕራብ ክልል ለዞን አስተዳደሮች የተሽከርካሪ ድጋፍ አደረገ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት ለዞን አስተዳደሮች የተሽከርካሪ ድጋፍ አደረገ፡፡
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ ለሥድስቱም ዞን አመራሮች እና ለቦንጋ ዳቦና ዱቄት ማምረቻ ፋብሪካ የተሽከርካሪዎቹን ቁልፍ አስረክብዋል።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በቅልፍ ርክክቡ ወቅት÷ ተሽከርካሪዎቹ ለመንግስታዊ ሥራ ብቻ አገልግሎት ላይ እንዲውሉ አሳስበዋል።
ለሁሉም ዞኖች አንድ አንድ ተሽከርካሪ ድጋፍ መደረጉን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡
እንዲሁም በቅርቡ በቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት ለተመረቀው የቦንጋ ዳቦና ዱቄት ማምረቻ ፋብሪካም አንድ ተሽከርካሪ ድጋፍ መደረጉ ተገልጿል፡፡
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!