Fana: At a Speed of Life!

በሐዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክ የሚገኙ ድርጅቶች በቀን 10 ሺህ የአፍ መሸፈኛ ጭምብሎችን እያመረቱ ነው-ጠ/ሚ ዐቢይ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሐዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክ የሚገኙ ድርጅቶች በቀን 10 ሺህ የአፍ መሸፈኛ ጭምብሎችን እያመረቱ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ገለፁ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ በፌስቡክ ገፃቸው ባወጡት መረጃ፥ በኢትዮጵያ የሚገኙ ኢንዲስትሪዎች ወቅታዊውን ሁኔታ ከግሞት አስገብተው እየሠሩ ነው ብለዋል።

በዚህም በሐዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክ የሚገኙ ድርጅቶች ሥራቸውን ሳያስታጉሉ አስቸኳይ ፍላጎቶችን ለማሟላት እየተጉ መሆኑንም ገልፀዋል።

በአሁኑ ወቅትም በቀን 10 ሺህ የአፍ መሸፈኛ ጭምብሎችን እያመረቱ ሲሆን፥ የምርቱን መጠን በቀን ወደ 50 ሺህ ለማድረስ ማቀዳቸውንም ገልፀዋል።

የኢንዱስትሪዎቹን ስራ ያበረታቱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ “ሌሎች ድርጅቶችም ፈጠራ በታከለበት እና ለወቅቱ በሚያመች ሁኔታ ሥራቸውን እንዲከውኑ አበረታታለሁ” ብለዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.