Fana: At a Speed of Life!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አዳዲስ ሹመቶችን አጸደቀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አዳዲስ ሹመቶችን አጽድቋል፡፡

ሹመቶቹ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔ እየተካሄደ በሚገኝበት ወቅት ነው፡፡
በዚህም ፡-

1. ዶክተር ጀማሉ ጀንበሩ – በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአረንጓዴ ውበትና ልማት ቢሮ ሃላፊ

2. አቶ ቢኒያም ምክሩ – የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ሃላፊ

3. አቶ አብርሃም ታደሰ – የአዲስ አበባ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ ሃላፊ

4. አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን – የፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ

5. አቶ አደም ኑሪ – የገቢዎች ቢሮ ሃላፊ

6. አቶ በላይ ደጀን – የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ

7. ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ – የአዲስ አበባ የቴክኒክና ትምህርት ስልጠና ቢሮ ሃላፊ

8. አቶ ካሳሁን ጎንፋ – የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዋና ስራ አስፈጻሚ

9. አቶ አያሌው መላኩ – የመሬት ይዞታ ማስለቀቅና አቤቱታ ሰሚ ጉባዔ ሃላፊ

10. ወ/ሮ እናታለም መለሰ – የአዲስ አበባ የኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ ሆነው ሹመታቸው በሙሉ ድምፅ ጸድቋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ተሿሚዎቹ ቃለ መሃላ ፈጽመዋል ።

በመሳፍንት እያዩ

#Ethiopia #AddisAbaba

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.