Fana: At a Speed of Life!

የተባበሩት መንግስታት የሴቶችን ጫና ለመቀነስ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር እየሰራሁ ነው አለ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግስታት የስነ ህዝብ ድጋፍ (ዩኤንኤፍፒኤ) የሴቶችን ጥቃት ለመከላከል እና በስነ ተዋልዶ ተጋላጭ የሆኑ ሴቶችን ጫና ከመቀነስ አንፃር ከመንግስት ጋር እየሰራ መሆኑን ገለጸ፡፡

ዩኤንኤፍፒኤ ፥ በኢትዮጵያ 50ኛ ዓመቱን ባከበረበት ወቅት የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስትር ዲዔታ ሰመሪታ ሰዋሰውና የድርጅቱ የምስራቅ አፍሪካ እና ደቡብ አፍሪካ ዳይሬክተር ሊድያ ዚጎሞ ተገኝተዋል።

ወይዘሮ ሰመሪታ ሰዋሰው÷ ድርጅቱ በኢትዮጵያ ላይ እያከናወናቸው ያሉትን ተግባራት በማድነቅ በቀጣይነት መንግስት አስፈላጊውን ትብብር እንደሚያደርግ ገልፀዋል።

የምስራቅ አፍሪካ እና ደቡብ አፍሪካ ዳይሬክተር ሊድያ ዚጎሞ በበኩላቸው ÷ ድርጅቱ በኢትዮጵያ የሴቶችን ጥቃት በመከላከል፣ የእናቶችን ሞት በመቀነስ፣ ያለአቻ ጋብቻን በማስቀረት ረገድ አበረታች ውጤት ማስመዝገቡን ተናግረዋል።

የተባበሩት መንግስታት የስነ ህዝብ ድጋፍ ፥ በፈረንጆቹ 1973 በመመስረት በስነ ተዋልዶ፣ በቤተሰብ ምጣኔ፣ በእናቶች ጤና እንክብካቤ፣ ፆታን መሰረት ያደረገ ጥቃትን በመከላከል ላይ የሚሰራ የተራድኦ ተቋም ነው።

በታሪኩ ወ/ሰንበት

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.