Fana: At a Speed of Life!

በማላዊ በተከሰተው ከባድ አውሎ ንፋስ የ447 ሰዎች ህይዎት አለፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡባዊ ማላዊ በተከሰተው ከባድ አውሎ ንፋስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 447 መድረሱ ተገለፀ፡፡

በትላንትናው እለት በማላዊ ሰዓት አቆጣጠር 7 ሰዓት አካባቢ የደረሰው ከባድ አውሎ ንፋስ(ሳይክሎን) በሀገሪቱ ዜጎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አደርሷል፡፡

በደቡባዊ ማላዊ በተከሰተው አደጋ የሟቾች ቁጥር 447 የደረሰ ሲሆን ፥ ከ362 ሺህ በላይ ዜጎች ደግሞ መፈናቀላቸው ነው የተገለፀው፡፡

የሀገሪቱ የአደጋ አስተዳደር ጉዳዮች ቢሮ እንዳስታወቀው ፥ በአደጋው በተጨማሪ 918 ዜጎች ሲቆስሉ 282 ሰዎች ደግሞ የደረሱበት አልታወቀም፡፡

የማላዊ መከላከያ ሰራዊት፣ የፖሊስ አባላትና እና የነፍስ አድን ስራተኞች ዜጎችን ለማዳን ርብርብ እያደረጉ ሲሆን ፥ የህክምና ሰራተኞችንና የህክምና ቁሳቁሶችን ጉዳቱ ወደተከሰተበት አካባቢው እያደረሱ ነው ተብሏል፡፡

የማላዊው ፕሬዚዳንት ላዛሩስ ቻክዌራ  ÷ ለአደጋው ባቀረቡት የድጋፍ  ጥሪ መሰረት የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ ኩባንያዎችና ግለሰቦች እንዲሁም የተለያ ሀገራት መንግስታት  ምላሽ መስጠታቸውን ገልፀዋል፡፡

በአውሎ ነፋሱ በተጎዱ አካባቢዎች ያለው ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑን የገለፁት ፕሬዚዳንቱ  ፥ ተጨማሪ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

የሀገሪቱ ትምህርት ሚኒስቴር በደቡብ ማላዊ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን ሲዘጋ ፥ በአካባቢው የሚገኙ 230 ትምህርት ቤቶች ለተፈናቀሉ ሰዎች ማቆያነት እንዲውሉ ይደረጋል ማለቱን ሲጂቲኤን ዘግቧል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.