Fana: At a Speed of Life!

በሶል ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ኮሪያ በተካሄደው የ77ኛው ሶል ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል፡፡

በውድድሩ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ርቀቱን አጠናቀዋል፡፡

በውድድሩ አትሌት አምደወርቅ ዋለልኝ 2 ሰዓት ከ5 ደቂቃ ከ26 ሴኮንድ በመግባት ቀዳሚ ሲሆን ፥ አትሌት ሺፈራው ታምሩ እና አትሌት ሀፍቱ አሰፋ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል፡፡

ባለፈው ዓመት በተካሄደው 76ኛው የሶል የወንዶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ሞስነት ገረመው አሸናፊ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.