Fana: At a Speed of Life!

የገቢ ንቅናቄ ማስጀመሪያና የእውቅና አሰጣጥ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ “ግብር ለሀገር ክብር” በሚል መሪ ሀሳብ የገቢ ንቅናቄ ማስጀመሪያና የግብር ከፋዮች እውቅና አሰጣጥ መርሐ ግብር እያካሄደ ነው፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የገቢዎች ሚኒስትር ወይዘሮ አይናለም ንጉሴ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ሌሎች የመንግስት የስራ ሀላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ በ2014 የግብር ዘመን የሚጠበቅባቸውን የግብር ግዴታ በታማኝነትና በወቅቱ ለተወጡ 300 ግብር ከፋዮች ዕውቅና እና ሽልማት እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡

በየሻምበል ምህረት

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.