Fana: At a Speed of Life!

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ያለው እንቅስቃሴ አበረታች መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢንዱስትሪ ፓርኮች ያለው የሥራ እንቅስቃሴ አበረታች መሆኑን የአሜሪካ የውጭ ንግድ ጉዳይ ካውንስለሮች ገለጹ፡፡

በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ የውጭ ንግድ ጉዳይ ካውንስለሮች ቡድን በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለውን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።

ካውንስለሮቹ ከአጎዋ ተጠቃሚነት ዕድል መቋረጥ ጋር ተያይዞ ባጋጠሙ ተግዳሮቶች ላይ በፓርኩ ከሚሠሩ ባለሀብቶች ጋር መክረዋል፡፡

በፓርኩ ከ22 በላይ ዓለም አቀፍ ባለሀብቶች ኢንቨስት በማድረግ ከ27 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠራቸውን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን መረጃ ያመላክታል ።

#Ethiopia #industrialparksdevelopmentcorporation #america #AGOA
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.