Fana: At a Speed of Life!

ከለውጡ በኋላ የተገኙ ድሎች እና ስኬቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል- የምስራቅ ቦረና እና ኢሉ አባቦር ዞኖች ነዋሪዎች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና እና ኢሉ አባቦር ዞኖች የተለያዩ አካባቢዎች ከለውጡ በኋላ የተገኘውን ድልና ስኬት ለማስቀጠል ያለመ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል፡፡

የድጋፍ ሰልፉ ተሳታፊዎች ከመጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ወዲህ በክልሉ የተመዘገቡ ድልና ስኬቶችን የሚያንጸባርቁ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል፡፡

ከለውጡ በኋላ የተገኙ ድሎች እና ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የድጋፍ ሰልፉ ተሳታፊዎች ተናግረዋል፡፡

በድጋፍ ሰልፉ በርካታ ቁጥር ያላቸው በዞኖቹ የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል፡፡

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.