Fana: At a Speed of Life!

አቶ ማሞ ምሕረቱ ከጣልያን ባንክ ምክትል ገዥ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ ከጣልያን ባንክ ምክትል ገዥ ፒዬሮ ሲፖሎንጋር ተወያዩ፡፡

ውይይቱን ያካሄዱት ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም እና የዓለም ባንክ የ2023 የፀደይ ወቅት ስብሰባ ጎን ለጎን ነው፡፡

በውይይታቸውም÷ በዘርፉ ያሉ አሠራሮችን ለማጎልበት የጣልያን ባንክ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በክፍያ ሥርዓት፣ ማክሮ እና ስታትስቲክስ ዙሪያ የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ተስማምተዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ በትናንትናው ዕለትም÷ ከኬንያ፣ ዛምቢያ፣ ሞዛምቢክ እና ዩጋንዳ ማዕከላዊ ባንኮች ገዥዎች ጋር መወያየታቸው ይታወሳል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.