Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ሺ ጂን ፒንግ ከዩክሬን ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂን ፒንግ ከዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ጋር በስልክ ተወያይተዋል፡፡

የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ውይይት የዩክሬን እና ሩሲያ ጦርነት ከተጀመረ ወዲህ የተደረገ የመጀመሪያ ውይይት መሆኑ ተገልጿል፡፡

ፕሬዚዳት ሺ ÷በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያጠናክር ልዑክ ወደ ኬቭ ለመላክ ማቀዳቸውን ገልፀዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ በበኩላቸው ÷ ቻይና በኬቭ ዲፕሎማቶችን ለመላክ ማቀዷ የሁለቱን ሀገራት ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የሚያጠናክር መሆኑን በትዊተር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

ውይይቱ በፕሬዚዳንት ዘለንስ ግብዣ የተደረገ ሲሆን ፥ የዩክሬን እና ሩሲያ ጦርነት መፍትሄ እንዲያገኝ ቻይና ሚናዋን እንደምትወጣ አስታውቃለች፡፡

እየተካሄደ ባለው የዩክሬን እና ሩሲያ ጦርነት ቻይና ገለልተኛ አቋም እንዳላትና ጦርነቱ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ስትገልፅ መቆየቷን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.