Fana: At a Speed of Life!

“ኦሬንጅ”በቴሌኮሙ ዘርፍ በኢትዮጵያ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) “ኦሬንጅ” የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት አቅራቢ በዘርፉ በኢትዮጵያ የመሠማራት ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ፡፡

የኢፌዴሪ ገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በመካከለኛው ምሥራቅ እና በአፍሪካ በቴሌኮም ዘርፍ ላይ የተሠማራውን የ“ኦሬንጅ” ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ጀሮም ሄኒክ በቢሯቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡

ሚኒስትር ዴኤታው ÷ በኢትዮጵያ በቴሌኮሙኒኬሽኑ ዘርፍ ያለውን የኢንቨስትመንት አማራጮች ገልጸውላቸዋል፡፡

የኢፌዴሪ መንግስት ባለፉት ሁለት ዓመታት ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና በቴሌኮሙ ዘርፍ ከውጭ ባለሐብቶች ጋር ለመሥራት ያሳየውን ቁርጠኝነትም አንስተው ፤ በጋራ ሊሠሩባቸው በሚችሉባቸው ሁኔታዎች ላይ መክረዋል፡፡

ለአብነትም ፥ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን በኢትዮጵያ ሥራ መጀመር እና የኢትዮ ቴሌኮምን ትራንስፎርሜሽን ማንሳታቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

የኦሬንጅ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጀሮም ሄኒክ በበኩላቸው ፥ ኮርፖሬሽኑ በአፍሪካ የቴሌኮም ገበያ ውስጥ መዋዕለ-ንዋዩን አፍስሶ ያስመዘገበው ስኬት አብራርተዋል።

በቀጣይም “ኦሬንጅ” በዘርፉ ሥራዎቹን ዕውን ለማድረግ በሚችልባቸው ቴክኒካል ጉዳዮች ላይ ለመወያየት ጊዜ ቀጥሯል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.