Fana: At a Speed of Life!

ኤጀንሲው ከ2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃና አገልግሎት ኤጀንሲ 2 ቢሊየን 847 ሚሊየን በላይ ብር ገቢ መሰብሰቡን ገለጸ፡፡

የኤጀንሲው ዳይሬክተር ሀሰን ሞሳ እንዳስታወቁት ÷ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 2 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ነው 2 ቢሊየን 847 ሚሊየን 951 ሺህ 691 ብር የተሰበሰበው፡፡

ገቢው 105 ሺህ 612 ለሚሆኑ ተገልጋዮች ልዩ ልዩ አገልግሎቶች በመስጠት የተሰበሰበ መሆኑን ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል፡፡

ተቋሙ ለዚህ ስኬት የበቃው የአገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ሁሉንም ተገልጋዮች በአጭር ጊዜና ቀልጣፋ በሆነ መልኩ ማስተናገድ በመቻሉ እንደሆነ መናገራቸውንም ከኤጀንሲው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.