Fana: At a Speed of Life!

የኔዘርላንድሱ “ቪኦን.ቴሌኮም” በኢትዮጵያ እንዲሠራ ጥሪ ቀረበለት

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኔዘርላንድሱ “ቪኦን.ቴሌኮም” በኢትዮጵያ እንዲሠራ ጥሪ ቀረበለት፡፡

የኢፌዴሪ ገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከ“ቪኦን.ቴሌኮም” ግሩፕ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ማቲው ጋልቫኒ ጋር በበይነ-መረብ ተወያይተዋል፡፡

በውይይቱም የቪ ኦን ቴሌኮምን ጥልቅ የሥራ ልምድ በማድነቅ ኩባንያው ልምዱን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ቢሰራ ውጤታማ እንደሚሆንም ገልጸውላቸዋል፡፡

የ“ቪኦን. ቴሌኮም” ግሩፕ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ማቲው ጋልቫኒ በበኩላቸው ÷ የኢትዮጵያን ምጣኔ ሐብት ለማሳደግ እየሠፋ በመጣው የሥራ ዕድል መደነቃቸውን ገልጸዋል፡፡

የ“ቪኦን”ን የገበያ ዕድል እና አማራጮች የማሥፊያ ሥልቶችንም ከልምዳቸው አካፍለዋል፡፡

ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) የ“ቪኦን.ቴሌኮም” ግሩፕ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ማቲው ጋልቫኒ ኢትዮጵያን እንዲጎበኙ እና ያሉትን የቢዝነስ አማራጮች በአካል እንዲቃኙ ጋብዘዋል፡፡

ሚኒስትር መሥሪያ ቤቱ በቴሌኮሙኒኬሽኑ ዘርፍ በኢትዮጵያ መዋዕለ-ንዋያቸውን ማፍሰስ ከሚፈልጉ አካላት ጋር ለመሥራት ግንኙነቱን መቀጠሉን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.