Fana: At a Speed of Life!

የዓለም የትምህርት ትብብር ድርጅት ዋና መስሪያ ቤቱን በአዲስ አበባ ከፈተ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 10 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም የትምህርት ትብብር ድርጅት ዋና መስሪያ ቤቱን በአዲስ አበባ በዛሬው ዕለት በይፋ ከፈተ።

በሥነ-ሥርዓቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ምስጋኑ አርጋ፣ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ የድርጅቱ ዋና ጸሐፊ መንሱር ቢን ሙሳላም እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

የዋና መስሪያ ቤቱ ስራ መጀመርም ኢትዮጵያ ከዓለም የትምህርት ትብብር ድርጅት ጋር ያላትን ትብብር ለማሳደግ እንደሚያስችል ተመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.