ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መመለሱን አረጋገጠ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ6 አመታት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መመለሱን አረጋግጧል
ቤንች ማጂ ቡና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ 2ለ1 በመረታቱ ነው ንግድ ባንክ 2 ጨዋታዎች እየቀሩት ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ማደጉን ያረጋገጠው፡፡
በኢትዮጵያ እግርኳስ የቀደመ ስም ያለው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ2009 ከፕሪሚየር ሊጉ ወደ ከፍተኛ ሊግ ወርዶ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡