Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ በትራፊክ አደጋ የ2 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)በአዲስ አበባ ንፋስ ሥልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት አለፈ።

የትራፊክ አደጋው የደረሰው በወረዳ 11 ልዩ ሥሙ አትክልት ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መሆኑን የወረዳው ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

ሕይወታቸውን ካጡት ሁለት ሰዎች በተጨማሪ በሌሎች ሁለት ሰዎች ላይ ደግሞ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱንና በህክምና ክትትል ላይ እንደሚገኙም ተገልጿል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.