Fana: At a Speed of Life!

የአማራ ክልል የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች የግብርና እና ሳይንስ አውደ ርዕይን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እና የግብርና ባለሙያዎች በሳይንስ ሙዚየም በመገኘት በግብርና ሚኒስቴር የተዘጋጀውን የግብርና እና ሳይንስ አውደ ርዕይ ጎብኝተዋል።

ዐውደ ርዕዩ ፥ የቴክኖሎጂ ዕውቀትን ለማሸጋገርና እና ምርታማነትን ለማሳደግ ትልቅ ተሞክሮ የሚወሰድበት መሆኑን የጉብኝቱ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ግብርናን በቴክኖሎጂ በማዘመን ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ሊሠራ እንደሚገባም መገለጹን የዘገበው አሚኮ ነው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.