Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ ሜዳ ቴኒስ ስፖርተኞች ልዑካን ቡድን ሽኝት ተደረገለት

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በተለያዩ ሀገራት አስተናጋጅነት በሚዘጋጀው የሜዳ ቴኒስ ውድድር ላይ የሚሳተፉ የኢትዮጵያ ስፖርተኞት ልዑካን ቡድን ሽኝት ተደረገለት።

በኮንጎ ኪኒሻሳ እና በሩዋንዳ አዘጋጅነት በሚደረጉት የሜዳ ቴኒስ ሻምፒዮና እና ዓለምአቀፍ ውድድሮች ላይ የሚሳተፉት የወንዶች እና የሴቶች የስፖርት ልዑካን ቡድን ሽኝት እና የእራት ግብዣ ተደርጎላቸዋል።

የአትሌቲክስ ቡድኑ ከ25 ዓመታት በኋላ ነው በዓለምአቀፉ የሜዳ ቴኒስ ውድድር ላይ የሚሳተፈው።

የኢትዮጵያ ቴኒስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሚካኤል ንጉሴ ÷ አትሌቶቹ ከተሳትፎ ባለፈ ውጤት ይዘው እንዲመለሱ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በሁለቱ ሀገራት የሚደረገው የዓለም ሜዳ ቴኒስ ሻምፒዮና ከነገ ጀምሮ በሩዋንዳ ኪጋሊ እንደሚካሄድ ፌዴሬሽኑ አስታውቋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.