Fana: At a Speed of Life!

በአቶ ደመቀ መኮንን የተመራ ልዑክ ሳዑዲ ዓረቢያ ሪያድ ገባ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የተመራ ልዑክ ሳዑዲ ዓረቢያ ሪያድ ገብቷል፡፡

ልዑካኑ ኪንግ ካሊድ አውሮፕላን ማረፊያ ሲድርስ የሳዑዲ ዓረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ በሳዑዲ ዓረቢያ የኢፌዴሪ አምባሳደር ሌንጮ ባቲ እና የኤምባሲው ሰራተኞች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

የልዑካን ቡድኑ አባላት በሳዑዲ በሚካሄደው አይ ኤስ አይ ኤስ የሽብር ቡድንን ለመዋጋት ከተቋቋመው ዓለም አቀፍ ጥምረት የሚኒስትሮች ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ነው ሪያድ የገቡት፡፡

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.