የታይዋን የአየር ፣ የምድር እና የባሕር ኃይል በተጠንቀቅ እንዲጠብቁ ታዘዙ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት ታይዋንን እና ቻይናን በሚለየው ሰርጥ አካባቢ 10 የቻይና የጦር አውሮፕላኖች ታይተዋል በሚል የአየር ፣ የምድር እና የባሕር ኃይሏ ክትትል እንዲያደርግ ታይዋን አዘዘች፡፡
በዚህም መሠረት የጦር አውሮፕላኖቿ ፣ መርከቦቿ እና የምድር ሚሳኤሎቿ በተጠንቀቅ እየተጠባበቁ ነው ተብሏል፡፡
ታይዋን ከሣምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ 37 የሚደርሱ የቻይና የጦር አውሮፕላኖች ወታደራዊ እንቅስቃሴ እያደረጉ ነው ብላ ስታሳውቅ ይህ ሁለተኛ ጊዜ መሆኑን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!