የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መገጣጠሚያ ፋብሪካ ሥራ ጀመረ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በደብረ ብርሃን ከተማ የተገነባው የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መገጣጠሚያ ፋብሪካ መገጣጠም ጀመረ።
ፋብሪካው በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ሚኒባስ፣ መለስተኛ አውቶቡስ እና የከተማ አውቶቡስ ተሽከርካሪዎችን ማምረት መጀመሩን የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሰጠኝ እንግዳው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል።
ፋብሪካው በመጀመሪያ ዙር 216 ሚኒባሶችን በደብረብርሃን እና ገላን ገጣጥሞ ለገበያ ለማቅረብ እየሠራ መሆኑንም ነው የገለጹት።
በደብረ ብርሃን ከተማ ለተገነባው በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ተሸከርካሪዎች መገጣጠሚያ ፋብሪካ 2 ቢሊየን ብር ወጪ መደረጉን አቶ ሰጠኝ ተናግረዋል፡፡
በዘላለም ገበየሁ
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!