Fana: At a Speed of Life!

በአማራ ክልል የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል ሁለተኛው ምዕራፍ የመጀመሪያ ዙር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በደቡብ ጎንደር ዞን ደራ ወረዳ ጎሃ ቀበሌ እየተካሄደ ይገኛል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር)፣ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ኢያሱ ኤልያስ (ፕ/ር) እና የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ ኃይለማርያም ከፍያለው (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች ተገኝተዋል።

በአማራ ክልል በሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ የመጀመሪያው ዓመት 1 ነጥብ 6 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ግብ ተይዞ ወደ ሥራ መገባቱ ተገልጿል።

በክልሉ ለደን እና ለምግብነት የሚያገለግሉ የፍራፍሬና ሌሎች ችግኞች ላይ ትኩረት ተደርጎ የሚካሄደው የችግኝ ተከላ ከ201 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት እንደሚሸፈን መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

በክልሉ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በተሰራው ተከታታይ ሥራ የደን ሽፋኑ 16 በመቶ ደርሷል ተብሏል፡፡

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.