Fana: At a Speed of Life!

የተመድ የስነ-ሕዝብ ፈንድ ከኢትዮጵያ  ጋር ያለው ትብብር እንደሚያጠናክር ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)  አዲስ ከተሾሙት የተባባሩት መንግስታት ደርጅት የስነ-ሕዝብ ፈንድ የኢትዮጵያ ተወካይ ኮፊ ኩዋሜ ጋር ተወያይተዋል፡፡

ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)÷ተወካዩ በቆይታቸው በስነ-ሕዝብ ዘንድ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለማጠናከር ትብብራቸውን እንደሚያጎለብቱ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡

መንግስት የስነ-ሕዝብን ጉዳይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑ ጠቅሰው÷በሀገሪቱ የልማት እቅዶች ውስጥ በማካተት እተገበረ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

ኮፊ ኩዋሜ በበኩላቸው ÷ የተባበሩት መንግስታት የስነ-ሕዝብ ፈንድ ከኢትዮጵያ መንግስትና ሕዝብ ጋር በስነ-ሕዝብ ጉዳዮች ዙሪያ የሚሰራቸውን የትብብር ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ ቆይታቸው የሕዝብን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ የትብብርና የልማት አጋርነት ተግባራትን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.