የተመድ የስነ-ሕዝብ ፈንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ትብብር እንደሚያጠናክር ገለጸ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) አዲስ ከተሾሙት የተባባሩት መንግስታት ደርጅት የስነ-ሕዝብ ፈንድ የኢትዮጵያ ተወካይ ኮፊ ኩዋሜ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)÷ተወካዩ በቆይታቸው በስነ-ሕዝብ ዘንድ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለማጠናከር ትብብራቸውን እንደሚያጎለብቱ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡
መንግስት የስነ-ሕዝብን ጉዳይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑ ጠቅሰው÷በሀገሪቱ የልማት እቅዶች ውስጥ በማካተት እተገበረ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
ኮፊ ኩዋሜ በበኩላቸው ÷ የተባበሩት መንግስታት የስነ-ሕዝብ ፈንድ ከኢትዮጵያ መንግስትና ሕዝብ ጋር በስነ-ሕዝብ ጉዳዮች ዙሪያ የሚሰራቸውን የትብብር ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ ቆይታቸው የሕዝብን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ የትብብርና የልማት አጋርነት ተግባራትን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡