Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ እና ቻይና በታዳሽ ኃይል ልማት ላይ በጥምረት የሚያከናውኑትሥራ ተደነቀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና ቻይና በታዳሽ ኃይል ልማት ላይ በጥምረት እያከናወኑ የሚገኘውን ሥራ የተመድ የልማት ፕሮግራም (ዩ ኤን ዲፒ) አደነቀ፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም÷ በ “ግሎባል ደቡብ” መርሐ-ግብር በተመጣጣኝ ዋጋ ታዳሽ ኃይልን ለማስተዋወቅ ከቻይና ጋር የመሠረትኩት አጋርነት ይበል የሚያሠኝ ነውም ብሏል፡፡

ድርጅቱ በኢትዮጵያ የተጀመረውን የታዳሽ ኃይል ተደራሽነትን የማሥፋት መርሐ-ግብር ወደ አፍሪካ ሀገራት ማሥፋት እንደሚገባ ገልጿል፡፡

የተመድ የልማት ፕሮግራም በኢትዮጵያ ምክትል ተወካይ ክሊፋስ ቶሮሪ ÷ በቻይና እና በኢትዮጵያ መካከል በዘላቂ የኃይል አጠቃቀም ላይ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች ይደነቃሉ ማለታቸውን ሲ ጂ ቲ ኤን ዘግቧል፡፡

የታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂን ከማስተዋወቅ አንጻርም ባዮጋዝ እና ከፀሐይ የሚገኝ ኃይልን ማስተዋወቅ እና በሥፋት መጠቀም ወሳኝ ስለመሆኑ አስገንዝበዋል፡፡

ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር በመተባበ ግብርና-መር ኢንዱስትሪውን በመጠቀም ታዳሽ ኃይል ላይ እያከናወነች ያለውን ሥራም አወድሰዋል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የደቡብ – ደቡብ ትብብርን ለመደገፍ፣ ከኢትዮጵያ እና ቻይና ጋር በሦስትዮሽ የትብብር ማዕቀፍ በጋራ ለመሥራት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.