Fana: At a Speed of Life!

አትሌት ገንዘቤ በአንትሪም ኮስት ግማሽ ማራቶን እንደምትሳተፍ  አስታወቀች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ገንዘቤ ዲባባ በሰሜናዊ አየርላንድ አንትሪም ኮስት በሚካሄደው ግማሽ ማራቶን እንደምትሳተፍ አረጋግጣለች፡፡

አትሌት ገንዘቤ በማኅበራዊ ትስስር ገጿ ባሰፈረችው መልዕክት÷ ነሐሴ 27 በሚካሄደው የአንትሪም ኮስት ማራቶን እንደምሳተፍ ስገልፅ በከፍተኛ ደስታ ነው ብላለች፡፡

ከዚህ በፊት በአየርላንድ አንተሪም ኮስት ተሳትፋ እንደማታውቅም ነው የገለጸችው፡፡

አድናቂዎቿ በተጠቀሰው ቀን እና ቦታ ተገኝተው እንዲያበረታቷትም ጠይቃለች፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.