Fana: At a Speed of Life!

ከ153 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የፌዴራል ፖሊስ የምዕራብ ፈጥኖ ደራሽ ካምፕ ተመረቀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሶሳ ከተማ ከ153 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባውን የፌዴራል ፖሊስ የምዕራብ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ካምፕ ተመረቀ፡፡

በ2007 ዓ.ም ግንባታው የተጀመረው ካምፑ÷ የመኝታ፣ የእንግዳ ማረፊያ፣ ክሊኒክ እና የተለያዩ የስፖርት ማዘውተሪያዎችን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን÷ ካምፑ በክልሉ ያለውን ሠላም ዘላቂ ለማድረግ እየተደረገ ላለው ጥረት ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል፡፡

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል የወቅቱ የምስራቅ አፍሪካ ፖሊስ አዛዦች ሕብረት ድርጅት ፕሬዚዳንት÷ ሠላም የማስከበር ሥራዎችን ለማጠናከር በክልሎች መሠል ካምፖችን ወደሥራ እያስገቡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ቀጠናውን ከየትኛውም የጸረ-ሠላም እንቅስቃሴ ነጻ በማድረግ ሠላሙን ለማረጋገጥ የፌዴራል ፖሊስ ተልዕኮውን ይወጣል ማለታቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡

የፌዴራል ፖሊስ እና የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በካምፑ ግቢ አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.