Fana: At a Speed of Life!

የፊታችን ሐምሌ 8 ቀን የኢትዮጵያ የፕሪሚየር ሊግ ተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ይከፈታል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከፊታችን ሐምሌ 8 ቀን ጀምሮ የኢትዮጵያ ወንዶች እና ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ተጫዋቾች የዝውውር መስኮት እንደሚከፈት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስታወቀ፡፡

የዝውውር መስኮቱ ከሐምሌ 8 ቀን እስከ መስከረም 25 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ ተገልጿል፡፡

የተጫዋቾች ዝውውር ሕጋዊነት የሚፀድቀውም÷ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ጽሕፈት ቤት ተገኝቶ በመፈራረም ብቻ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

በክልል እግር ኳስ ፌደሬሽኖች እና በሌላ አካል በኩል የሚደረግ ስምምነት ተቀባይነት የለውም መባሉን   የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.